top of page
Search

ኢትዮጵያ የመተንፈሻ ቀዳዳ የተሰራላቸው ማስኮችን ወደ ሀገር እንዳይገቡ አገደች።

  • Ethio-Daily ኢትዮ- ወቅታዊ
  • Jun 22, 2020
  • 1 min read

ኢትዮጵያ የመተንፈሻ ቀዳዳ የተሰራላቸው ማስኮችን ወደ ሀገር እንዳይገቡ አገደች።

የኢትዮጲያ ምግብ እና መድሀኒት ቁጥጥር ባለስልጣን የኮሮና ቫይረስ ለመከላከል በሚል ጥቅም ላይ ከሚውሉ ማስኮች ውስጥ ቫልቭ ወይም የመተንፈሻ ቀዳዳ የተሰራላቸው ማስኮችን ወደ ሀገር እንዳይገቡ ትዕዛዝ ማስተላፉን አስታውቋል፡፡

ባስልጣኑ ከዚህ ቀደም ቫልቭ ወይም የመተንፈሻ ቀዳዳ የተገጠመላቸው ማስኮች የቫይረሱን ስርጭት ለመጨመር አስተዋፆ አላቸው በሚል ህብረተሰቡ እንዳይጠቀማቸው ማስታወቁ ይታወሳል፡፡

ነገር ግን ባለስልጣኑ ባስተላለፈው ትዕዛዝ መሰረት ህብረተሰቡ እነዚህን ማስኮች ከመጠቀም አልተቆጠበም እና ምን አይነት እርምጃዎች እየተወሰዱ ነው ሲል ኢትዮ ኤፍ ኤም ተቋሙን ጠይቋል፡፡ በባለስልጠኑ የመድሀኒት ምዝገበ እና ፍቃድ ዳይሬክተር አቶ አብደላ ቃሰው እነዚህ ቫልቭ ወይም የመተንፈሻ ቀዳዳ የተገጠመላቸው ማስኮችን ቫይረሱን ለመከላከል በሚል ዓላማ እናስገባ ለሚሉ ሰዎችም ሆነ ሀገር ውስጥ ለማምረት ፍቃድ ለሚጠይቁ ሰዎች ፈቃድ መስጠት አቁመናል ብለዋል፡፡ በተጨማሪም ቫይረሱን ለመከላል በሚል ዓላማ ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡም ለጉምሩክ ኮሚሽን ደብዳቤ መፃፉን ነግረውናል፡፡ እነዚህ ማስኮች ጥቅም ላይ እንዳይውሉ ሲደረግ የተሰሩበት ዓላማ በሽታውን ለመከላከል በሚል ባለመሆኑ እና ማስኮቹ በተገጠመላቸው የመተንፈሻ ቀዳዳ አማካኝነት ቫይረሱን ከመከላከል ይልቅ ለስርጭቱ ከፍተኛ አስተዋፆ ስለሚያደርጉ ማህበረሰቡ ማስኩን ከመጠቀም እንዲቆጠብ አሰጠንቅቀዋል፡፡

 
 
 

Recent Posts

See All
የላብራቶሪ ምርመራ

ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 3238 የላብራቶሪ ምርመራ አንድ መቶ ሰላሳ አንድ (131) ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 4663 ደርሷል።...

 
 
 

Comments


Post: Blog2_Post

Subscribe Form

Thanks for submitting!

+251947452470

©2020 by Ethio-Daily ኢትዮ- ወቅታዊ. Proudly created with Wix.com

bottom of page